Archive by Author | ethionetsanet

የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ መግለጫ (#አማርኛ)

==================================
የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ከመስከረም 26 እስከ ጥቅምት 2/ 2012 ዓ/ም ድረስ ለተከታታይ 7 ቀናት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በ2011 ዓ/ም ተይዘው የነበሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ዕቅዶች፤ ድርጅታዊና ፖለቲካዊ ስራዎች በተለይ ደግሞ በአዲሱ የፖለቲካ መድረክ የትግራይ ህዝብ ህልውና፣ ደህንነትና ዋስትና ለማስጠበቅ የተካሄደ ሁለንተናዊ የመመከት ትግል እና ይህንን መሰረት በማድረግ የተሰሩ ስራዎች በዝርዝር ገምግሟል፡፡ በዚህ ልዩ የትግል ምዕራፍ የታዩ ጥንካሬዎችንና ጉድለቶችን በመገምገም ሊወሰድ የሚችል ትምህርት በመለየት በዚህ ዓመት ሊሰሩ የሚገባቸው ልማታዊና ፖለቲካዊ ዕቅዶችንም አጽድቋል፡፡

በተጨማሪም አሁን ያለው ተጨባጭ አገራዊ ሁኔታዎችንና ዕድገቶችን በመገምገም በቀጣይ ለሚኖረው ትግል መሰረት ያደረገ የመመከትና ደህንነትን የማረጋገጥ አቅጣጫዎችንና ዕቅዶችን በዝርዝር ተወያይቶ በዚህ ዓመት ሊኖር የሚችለውን ሁለንተናዊ ትግል ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ስብሰባውን አጠናቋል፡፡
ባለፈው ዓመት ተይዘው የነበሩ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የሰላም ዕቅዶችን በቀጣይነት ለማስፋትና ለማጎልበት የሚያስችል ዘርፈብዙ ጥረት እየተካሄደ ቆይቷል፡፡ ከጀመርነው የፀረ- ድህነት ትግል ለአፍታም ሳንዘናጋ፣ በዋነኛው አጀንዳችን ላይ ለመረባረብ የሚያስችል አቅጣጫ ይዘን ሰፊ ርብርብ ስናደርግ ቆይተናል፡፡ በህዝባችን የተደራጀ ትግልና እንቅስቃሴ ከትክክለኛ መንገዳችን ሳንወጣ በልማት እቅዶቻችን ላይ ከፍተኛ ትኩረት በማድረግ ስንሰራ ቆይተናል፡፡

የሁሉም ዘመቻዎቻችንና ርብርቦቻችን ትኩረት የህዝባችን ደህንነትና ህልውና ከማስጠበቅ አንፃር እየቃኘንና ቅድሚያ ሰጥተን፣ የሁሉም ነገር ማጠንጠኛ ልማትና የህዝባችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መሆኑን በማመን ሁሉም ነገር ትተው ከነ አካቴው ወደ ጥፋት በገቡና ይባስ ብለው እኛንም ጎትተው ከመንገዳችን ሊያስወጡን በሚጥሩ ሀይሎች ሳንደናገር ስራችንን ማእከል አድርገን ከፍተኛ ርብርብ ስናደርግ ቆይተናል፡፡

ልማታዊ ዲሞክራሲያዊው መስመራችንን ጨብጠን የህዝባችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተለይ ደግሞ የወጣቶችንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማስፋት የሚያግዙ ተግባሮች በትግራይ እንዲከናወኑ ስናደርግ ቆይተናል።

ህዝባችን በየጊዜው የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ በመልካም አስተዳደር መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የቆዩ ችግሮች ፈትተን የህዝባችን ፍላጎቶች ለመመለስ የቀበሌን መዋቅር ለማስተካከል የተጀመረው የሪፎርም ስራ ተስፋ በሚሰጥ ደረጃ ወደ ተግባር ገብቷል፡፡ ስፋትና ጥልቀት ባለው ሁኔታ ሲደረግ የነበረው የወረዳ ሪፎርም ጥናትም ህዝባችን ልማትና ውጤታማ አገልግሎት እንዲያገኝ በሚያስችል መልኩ በዚህ ዓመት በከፍተኛ ትኩረት ለመፈፀም እንስቃሴ እየተደረገ ቆይቷል፡፡ ይህ በቀጣይ ለሚኖሩን ስራዎች እንደ አንድ ትልቅ መነሻ ሆኖ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ያግዛል፡፡

ይሁን እንጂ በልማት ስራዎቻችን በሚፈለገው መጠንና ስፋት በሚጠበቀው መጠን ውጤት ያላስመዘገብንባቸው ሁኔታዎች አሉ፡፡ በዋናነት በመልካም አስተዳደር ጉዳይ አሁንም ችግሮቻችን ሰፋፊ መሆናቸውን አይተናል፡፡ እየተጠራቀሙ በመጡ ችግሮች ሳቢያና በማስፈፀም አቅማችን ጉድለት ምክንያት ያልፈታናቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዳሉ እንገነዘባለን፡፡ በተለይም በወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይ አሁንም ሰፊ ችግር እንዳለ፣ በገጠርም በከተማም እየታየ ያለው የመሬት አስተዳደር ችግር፣ አገልግሎት በመስጠት ዙርያ ያለው ችግርና መንገላታት፣ ለልማት ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ዙርያ ያሉ መዘግየቶችና እንቅፋቶች እንዲሁም ሌሎች ተዛማጅ ችግሮች የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ በዝርዝር የተመለከታቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡
በመሆኑም እነዚህ ችግሮች በዚሁ ዓመት “በጊዜ የለም” መንፈስ እንዲፈቱ ከፍተኛ ጥረትና ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተመለክተናል፡፡ የልማት ስራችን የሁሉም ቋጠሮ መሆኑን በመገንዘብ፣ ለዘላቂ ህልውናችንና ደሕንነታችን መረጋገጥ ባለው ትርጉም ተገንዝበን በላቀ ቁርጠኝነትና ወኔ ልንዘምትና ልንገሰግስ ይገባል፡፡ ከዚህ የልማት እንቅስቃሴ የወጣቶችንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የላቀ ርብርብ ይደረጋል ብቻ ሳይሆን የእንቅስቃሴው አስኳል ይሆናል፡፡
ከዚህም አልፎ በእያንዳንዱ አከባቢ ያለው ፀጋ ግምት ውስጥ ያስገባ የልማት አደረጃጀትና ስምሪት እንዲደረግ እና በዚሁ ላይ የሚመሰረት በገጠርም ይሁን በከተማ ወደ አዲስ የልማት እንቅስቃሴ የሚያስገቡ አቅጣጫዎችንም የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ለይቷል፡፡ የተጀመረው የቀበሌና የወረዳ ሪፎርም ስራ ተጠናክሮ ወደ ተግባር እንዲገባና በመልካም አስተዳደር መሰረታዊ ለውጥ እንዲያመጣ እንቅስቃሴ እንዲደረግ የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አቅጣጫዎችን ለይቶ አስቀምጧል።

የተከበርክ የትግራይ ህዝብ፤

ባለፈው ዓመት በአንድ በኩል ፀረ ድህነት ትግል በማካሄድ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የትምክህት ኃይሎችን በመመከት ላይ ቆይተናል። የትግራይ ህዝብንና ህወሓትን ለማንበርከክ ከሁሉም አቅጣጫዎች ሲያጋጥመን የቆየው ፈተና ቀላል አልነበረም። እንደፈለግነው እንዳንሆን ማለፊያ የከለከሉን እና የጎን ውጋት እየሆኑብን ያሉት “የትግራይ ህዝብና ህወሓት ናቸው” ብለው ማለቂያ የሌለው ሴራና በደል ለመፈፀም ያልሞከሩት ፀረ-ህዝብ ተግባር አልነበረም።
ይሁን እንጂ ምኞታቸውና ዓላማቸው ስለተገነዘብን በትክክለኛ መንገድ ያደረግነው ፍትሃዊ ትግልና የመመከት ተግባር የጠላቶቻችን ምኞትና ህልም አምክነን ወደፊት እየተራመድን እንገኛለን። በህዝባችን ፅኑ አንድነትና ስምረት፣ በበሳል ንቃትና ምክንያታዊ ትግል፣ በማይነጥፍ ወኔ የተሳካ የመመከት ተግባር ስናከናውን ቆይተናል። ይህ ከትግራይ ህዝብ ጥረትና ትግስት ውጭ እንደማይሳካ እሙን ነበር። ያለፈው የሩቅና የቅርብ ታሪክህ እንደሚያሳየው ከትግልህና ከጥረትህ ውጭ መብትህንና ጥቅምህን ለማስከበር ፍቃድ የሚሰጥህ አካል አልነበረም፤ አሁንም አይኖርም።
ሁሉ ጊዜ ለፍትህና ለእኩልነት እንደቆምክ፣ ትክክለኛ መስመርህንና ዓላማህን ይዘህ በፅናት እየታገልክ፣ በሁሉም የትግል ምዕራፎች ያጋጠሙህ መሰናክሎችንና እንቅፋቶችን እየጠራረግክ በመጓዝ ላይ ትገኛለህ። ወደፊትም ብቸኛው መንገድህ ይህና ይህ ብቻ ነው። በዚህ እልህ አስጨራሽ የትግል ምዕራፍ ያካሄድከው ወደር የለሽ የመመከት ተግባር በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብ፤ በተለይም ደግሞ የትግራይ ወጣቶች፣ ምሁራንና ሴቶች ለፈፀማችሁትና እየፈፀማችሁ ላላችሁት ገድል የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ የተሰማውን ክብርና ኩራት በዚህ አጋጣሚ ሊገልጽላችሁ ይወዳል።

የተከበርክ የትግራይ ህዝብ

አሁንም ቢሆን ሁኔታዎች እየከበዱና እየባሱ በመምጣታቸው ደህንነትህንና ህልውናህን ለማስጠበቅ የምታደርገው ትግል ይበልጥ አጠናክረህ ልትቀጥልበት ይገባል፡፡ ሁሉም ህዝብ ሊገነዘበው የሚገባ ሃቅ ሊገጥመን የሚችለው ፈተና እና ፈተናውን ለመሻገር የሚጠይቀን ትግልና ጥረት እጅግ እየከበደ ሊመጣ ይችላል። ወደፊት መራመድ ሲያቅታቸው፣ በራሳቸው ድክመትና ፀረ-ህዝብ ተግባራቸው ፈተና ሲበዛባቸው ወደ ሌላ ወገን እየለጠፉ እያደናገሩ ዕድሚያቸውን ለማራዘም ጥረት ማድረጋቸው አይቀርም፡፡ አንድነትህንና ፅናትህን ለማደፍረስ በውስጣችን የሚታዩ ችግሮችን እንደ ዕድል ለመጠቀም እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ አልፎ አልፎ የሚታየውን ከባቢያዊነትም ይሁን በሃይማኖት ስም በመካከልህ ልዩነት ለመፍጠር ያላሳለሰ ተግባር እየፈጸሙ ይገኛሉ፡፡ ይህን ለማስጽፈፀም ታስቦ የሚላከው ባንዳ ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም፡፡ ይህ እንደሚሆን ተገንዝበህ እንደወትሮህ አንድነትህን አጠናክረህ፣ በአንድ ላይ ሆነህ ለላቀ ትግል ተዘጋጅ፡፡ የምንጊዜም ዋስትናህና የድል አድራጊነት ምስጢር አንድነትህ፣ መስመርህና ፅናትህ ነው፡፡ የትግራይ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ባለሃብቶችና ምሁራን አሁንም እንደቀድሞ በአንድነት ፀንታችሁ ሊኖረን ለሚችለው ትግል በላቀ ደረጃ ልትዘጋጁ ይገባል፡፡
መላው የድርጅቱ ኣባላትና አመራሮችም የላቀ ፅናትና ተነሳሽነት የሚጠይቀውን ትግል ህዝባችንን ይዘን ወደ ዘላቂ ድል ለመገስገስ መሪ ሚናችሁን ልትፈፅሙ ይገባል፡፡ ከዚህ ባለፈ የትግራይ ህዝብ ህልውናና ደህንነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ትግል የነበረውን የትግል አቅሞች ሁሉ ለማንቀሳቀስ ይሰራል፡፡ በትግራይ ውስጥ ካሉ ፖለቲካዊ ድርጅቶችና ሲቪክ ማህበራትም በጋራ ለመስራት ህወሓት የተለየ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ሊያረጋግጥላችሁ ይወዳል፡፡

የተከበርክ የትግራይ ህዝብ፤

የህወሓት ማእላዊ ኮሚቴ በስፋት ካያቸው መሰረታዊ ጉዳዮች አንዱ በሀገራችን እየታየ ያለው ፈጣን አደጋና ወዲፊትም ሊኖረው የሚችል አጠቃላይ ሁኔታ የሚመለከት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በአገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ ችግሮች እየተበራከቱ፣ ጥፋት በጥፋት ላይ እየተደራረበ፣ የጥፋቱ ስፋትና መጠን በየቀኑ እየጨመረ ወደ ከፋ አገር የመበተን ደረጀ እየደረሰ ነው፡፡ አደጋው ወደ ከፋ ደረጃ እንዲሄድ እያደረገ ያለው አንዱ ምክንያት የፓርቲ ውህደት ለመፈፀም እየተደረገ ያለው የችኮላ እንቅስቃሴ ነው፡፡ የፓርቲ ውህደት ጥያቄ በኢህአዴግ ውስጥ በተለያየ ጊዚያት እየተነሳ የቆየና ይህንን ለማድረግ ደግሞ ሊሟሉ የሚገባቸው መሰረታዊ ጉዳዮች እንዲታዩና በጥናት ላይ በመመስረት እንዲመለሱ መግባባት ላይ የተደረሰበት ጉዳይ ነው፡፡ ህወሓትም ቢሆን በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ የተለየ እምነት አልነበረውም፡፡ ሆኖም ግን ይህን ለማድረግ በሁሉም መሰረታዊ የመስመር ጥያቄዎች፣ ፕሮግራም፣ ስትራቴጂ ወደ አንድ የሚያስተሳስር አመለካካተና እምነት በሁሉም እህት ድርጅቶች ሲፈጠር ብቻ ነው መተግበር የሚችለው፡፡ አንድ ሊያደርግ የሚችል የጋራ የአመለካከትና የተግባር አንድነት በሌለበት ወቅት አንድ ድርጅት እንደ ድርጅት መጠን ህልውና ሊኖረው አይችልም፡፡ ከውህደት በፊት የሚያዋሃህድ አመለካከትና እምነት መለየት አለብን፡፡ ኢህአዴግንና አገርን እየበተኑ ካሉት የተገዙ ደባል አመለካከቶች የሚለይ መስመር እና አጥር በጠራ መልኩ ሳይለይና ሳይቀመጥ ውህደትን ማሰብ አይቻልም፡፡ በደፈረሰ አመለካከትና በአንድነት ሊሰምሩ በማይችሉ እሳትንና ጭድ አስተሳሰቦችን በተሸከመ ኢህአዴግ አይደለም ውህደት ቀርቶ በግምባርነት ለመቀጠል የማይችል የተበተነ ድርጅት ነው አሁን ያለው፡፡ እንደዚህ ያለ የተበተነ ድርጅት ወደ አንድ ፓርቲ ውህደት ይመጣል ብሎ ማሰብ በራሱ ድርጅቱን ከመበተን አልፎ አገርን የሚበትን ተግባር ነው ሊሆን የሚችለው፡፡

ከዚህም አልፎ በቅርቡ ከግንባሩ እምነትና መተዳደሪያ ደንብ ውጭ የፓርቲ ውህደት ለመፈፀም እየተደረገ ያለው ሩጫ ችግሩ እንዲባባስ የሚያደርግ ፀረ-ዲሞክራሲያዊ አካሄድ እየሰፋ መምጣቱን የሚያሳይ ነው፡፡ የቅርፅ ውህደት ብቻ ሳይሆን በይዘትና በያዘው ፕሮግራሙ በመሰረቱ የተለወጠ አዲስ ፓርቲ ለመመስረት ነው ጥረት እየተደረገ ያለው፡፡ ይህ ሲሆን የኢትዮጵያ ህዝቦች ኢህአዴግ ለያዘው ፕሮግራም መሰረት አድርገው የሰጡት አገርን የመምራት ስልጣን ያከትማል ማለት ነው፡፡ አገርን ለመምራት ሓላፊነት ያልተሰጠው አዲስ ፓርቲ እንዲመሰረት ነው እየተደረገ ያለው፡፡ እንዲህ ያለ አዲስ ፓርቲ በሃገራችን ፖለቲካዊ ድርጅቶች የምዝገባ ህግ ያላለፈ፣ በህዝቦች ፈቃደኝነት በስልጣን ላይ ለመቆየትም ሆነ ስልጣን ለመያዝ ለመወዳደር የማይችል ህገ-ወጥ ድርጅት ነው የሚሆነው፡፡
በመሆኑም በውህደት ስም በፍፁም ፀረ-ዴሞክራሲያዊ መንገድ አዲስ አሃዳዊ ድርጅት ሊመሰረት አይገባም፡፡ በሁሉም መለኪያዎች አንድ ፓርቲ ለመሆን የሚያስችል መነሻና ምክንያት በሌለበት ኢህአዴግን አፍርሶ ሌላ ፓርቲ ለማቋቋም ማሰብ አገርን የሚበትን ተግባር ነው፡፡ ስለዚህ ኢህአዴግ እንደ ግንባር ተደራጅቶ ችግሮችን በትግል እየፈታ አገር ሊመራ ይገባል፡፡ ከጊዜ አንፃርም ይህ ሊቆይ የሚገባው ጉዳይ ነው፡፡ አጋር ድርጅቶችም በውህደት ስም እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ህልውናችሁን የሚያጠፋ መሆኑን ልትገነዘቡ ይገባል፡፡ ይሁን እንጂ አጋር ድርጅቶች ወደ ኢህአዴግ በሙሉ አባልነት ገብታችሁ በጋራ ትግልና ጥረት አገርን የሚያድን ተግባር ሊትፈፅሙ እንደሚገባ ህወሓት በፅናት ያምናል፡፡ ከዚህ ውጭ ህወሓት በእንደዚህ ያለ አገርን የሚበትን ተግባር ውስጥ ገብቶ ሊንቦጫረቅ እንደማይፈልግ ሊታወቅ ይገባል፡፡ መላው የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች በውህደት ስም ኢህአዴግን ለማፍረስ የሚደረገው እንቅስቃሴ ሓላፊነት በተሞላበት ተገቢውን ትግል እንድታደርጉ ህወሓት ጥሪውን ያቀርብላችኋል፡፡

የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች

ህገ መንግስታችንና ህብረ ብሄራዊ ፌደራላዊ ስርዓታችን የሚሸረሽሩና የሚጥሱ ተግባራት በየቀኑ ማየት የተለመደ ተግባር ሆኗል። በዚሁ ወቅት የትምክህት ሐይሎች በአመለካከትና በተግባራዊ እንቅስቃሴ ጉልበት ፈጥረው አገር የሚያምሱበት ሁኔታ ተፈጥሯል። በብዙ የአገራችን አከባቢዎች የሰላም እጦት እየተስፋፋ፣ በዚሁም ምክንያት ከጊዜ ወደ ጊዜ መንግስት የማይቆጣጠራቸው አከባቢዎች እየተበራከቱ ይገኛሉ። ለመብቱና ለማንነቱ ለታገለ ህዝብ በርካታ ግፍና በደል የሚፈፀምበት፣ ዜጎች በእርጋታ የማይኖሩበት፣ በማንነታቸው ምክንያት በዜጎች ላይ ግፍ የሚፈፀምበት፣ ለህይወታቸውና ንብረታቸው ዋስትና ያጡበት፣ በዚች አገር ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ህውከትና መፈናቀል የተበራከተበት፣ መንግስት የዜጎች ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ እየተቸገረ የመጣበት፣ ከዚህ አልፎም የአገሪቱ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች እና የአማራ ክልል አመራሮች እስከመግደል ተግባር የተፈፀመበት፣ ሌላ ቀርቶ የነዚህ ምርጥ ጀነራሎችና መሪዎች ግድያ እንኳን በአግባቡ በማጣራት ለህዝብ ግልፅ ለማድረግ በማይቻልበት፣ የህግ በላይነት እየተጣሰ፣ የዜጎች ህይወት መጥፋትና መፈናቀል ማዳን የማይችል መንግስትና ስርዓት ወደ መሆን ተሸጋግረዋል ማለት ብቻ ሳይሆን ይህንን ለማስቆምና ለመግታትም ዋና ተግባሩ ያላደረገና ቁርጠኝነትም የሌለው ሆኗል።

የህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎችን ወደ ጎን በመተው ሌላ ጉዳይ ላይ በማትኮር የአገሪቱ ኢኮኖሚ እየተዳከመ ወደ ከፍተኛ ድቀትና ማሽቆልቆል እየገባ ነው። የአገሪቱ ልማት የሚመራውና የሚደግፈው አጥቶ፣ ልማታዊ አቅሞች እየመከነ፣ ስራ አጥነት እየተባባሰ፣ የህዝብ ኑሮ ውድነት ከጊዜ ወደ ጊዜ ሰማይ የሚሰቀልበት ሁኔታ ተፈጥሯል። በዚህ ምክንያትም ችግር በችግር ችግር እየተመሰቃቀለና እየተደራረበ በመሄድ ላይ ይገኛል። የህዝባችን ዋስትና የሆነው ህገ መንግስታችንና ህብረ ብሄራዊ ፌዴራል ስርዓታችን በማፍረስ አሃዳዊ ስርዓትን መልሶ ለመትከል እየሰራ ያለውና በዋናነት ይህንን አደጋና ጥፋት እየፈጠረና እየመራ የሚገኘው ትምክህተኛው ሀይልና በዙርያው የተሰባሰበ ፀረ ህዝብ ሐይል ነው።

በውስጣቸው ያለውን ድክመትና ፀረ-ህዝብ ተግባር ከመፍታትና ከማጥራት ይልቅ የሁሉም ችግር “ሶስተኛ ወገን አለው” የሚል የቆየ ዘፈን ሲደጋግሙ እየታየ ነው፡፡ ለአማራ ህዝብ የማይመለከተውና ያልተገባ ምስል እያስያዙና “ትምክህተኛ ተብለሃል!” እያሉ በዚህ ተሸፋፍነው በህዝቦች መካከል የቆየውን ዝምድናና ወንደማማችነት ለማደፍረስ እየጣሩ ይገኛሉ፡፡ የአማራ ህዝብ ትምክህተኞችን ታግሎ በእኩልነት የሚኖርባት አዲሲቷ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እንድትመሰረት የማይተካ ሚና የተጫወተ ህዝብ ነው፡፡ የትግራይና የአማራ ህዝቦች በጋራ ትግላቸው ትምክህተኛውን አሸንፈዋል፡፡ ለወደፊትም ቢሆን እነዚህ ህዝብ ለህዝብ አጋጭተው እንዲባላ በማድረግ መኖር የሚፈልጉና ሓላፊነታቸውን ትተው ለጥፋት የተሰማሩ ሓይሎች በተደራጀ መንገድ ሊታገላቸው ይገባል፡፡
መላው የሀገራችን ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦችም ህብረ-ብሄራዊ ፌዴራላዊ ስርዓታችንን ለማዳን በሚደረገው ወሳኝ ትግል ከማንኛውም ጊዜ በላይ አገራችንን ለማዳን ሊረባረብ ይገባል፡፡ሕብረ ብሄራዊ ፌዴራላዊ ሓይሎች የጀመራችሁትን ትግልና ሰፊ ትብብር መድረኮች አማራጭ የሌለው መሆኑን ተገንዝባችሁ ትግላችሁን አጠናክራችሁ ልትቀጥሉበት ይገባል፡፡ ህወሓትም የተጀመረውን ትግል ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚቻለውን ሁሉ እንደሚያደርግ ሊያረጋግጥላችሁ ይወዳል፡፡
በዚህ አጋጣሚ ሕገ-መንግስት፣ ሰላምና የህዝቦችና የአገርን ደሕንነት በመጠበቅ የላቀ ሓላፊነት ያለብህ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፤ አገራችን እያጋጠማት ያለውን አደጋ በሚገባ ተገንዝበህ ከጥፋት ለማዳን እያደረገው ያለው ርብርብ፣ ለዚች ልዩ ታሪክና ክብር ያላት ሃገር ሉኣላዊነቷንና ሰላሟን በመጠበቅ ረገድ ዛሬም እንደወትሮ በላቀ ደረጃ ህዝባዊ ሓላፊነትህን ተቋማዊ እንድትህን አጠናክረህ በምታደርገው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴም የትግራይ ህዝብና ህወሓት ከጎንህ ሆነው አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚፈፅሙ ልናረጋግጥ እንወዳለን፡፡

በህገ- መንግስቱ መሰረት ስድስተኛው አገር አቀፍና ክልላዊ ምርጫ በያዝነው ዓመት የግድ መካሄድ ያለበት ነው፡፡ በመሆኑም ህወሓትና የትግራይ ህዝብ ምርጫው በወቅቱ እንዲካሄድ በተደጋጋሚ አቋማቸውን እየገለፁ ቆይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ምርጫው ለማካሄድ የሚያስችል ምንም ዓይነት ዝግጅት እየተደረገ አይደለም፡፡ “በቂ ዝግጅት አላደረግንም” ተብሎ ምርጫውን ለማራዘም የሚደረገው ጥረት ፈፅሞ ተቀባይነት ሊኖሮው አይችልም፡፡ በአገራችን ያሉ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ነፃ የመወዳደር ዕድል አግኝተው ህዝብ በነፃ ፍላጎቱ የሚመርጠውን መንግስት ወደ ስልጣን እንዲመጣ በህዝብ ፍፁም ፈቃድ በስልጣን ላይ እንዲቆይ የሚያደርግ ህገ-መንግስታዊ መብት በጥብቅ መከበር አለበት፡፡ ይህ በማይሆንበት ወቅት መላው የአገራችን ህዝቦች መብታችሁንና ሕገ-መንግስታዊ ስልጣናችሁን አደጋ ላይ እየጣለ መሆኑን አውቃችሁ የላቀ ትግል ልታደርጉ በሚጠይቅ አስገዳጅ ጊዜ ላይ እንገኛለን።

የተከበርክ የኤርትራ ህዝብ
የትግራይና የኤርትራ ህዝብ ለጋራ መብትና ጥቅም በጋራ የታገሉ ወንድማማች ህዝቦች ናቸው፡፡ የነበረውና አሁንም ያለው ዝምድናና መደጋገፍ ወደ ዘላቂ አስተማማኝ ደረጃ ለማድረስ ባለፈው ዓመት የተጀመረው የሰላም ጭላንጭል በዚህ ዓመትም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል፡፡ በጋራ ለዘላቂ ሰላም ተደጋግፈን ልንሰራ ይገባል፡፡ የጀመርነው አዲስ እፎይታና ሰላም ዋስትና ያለው እንዲሆንም የሁለቱም ህዝቦች ትስስርና ግንኙነት እንዲጠናከር መስራት አለብን፡፡ የትግራይ ህዝብና ህወሓትም ይህንን ለማጠናከር ከነሱ የሚፈለገውን ሁሉ እንደሚፈፅሙ ደጋግመን ልናረጋግጥልህ እንወዳለን፡፡

የማንሻገረው ፈተና አይኖርም
ዘልአለማዊ ክብርና መጎስ ለስማእቶቻችን!
የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ
ጥቅምት 4/ 2012 ዓ/ም
መቐለ

72487475_2371247359611237_8243582347576868864_n

„Zählen Sie Ihre Hühner nicht, bevor sie geschlüpft sind“

                                         

Der neue äthiopische Ministerpräsident Dr. Abiy Ahmed hat sein Amt vor zwei Monaten angetreten, als das Land zum zweiten Mal in den Ausnahmezustand versetzt wurde, nachdem es in eine politische Kriese geraten ist, die sich in den letzten drei Jahren abgezeichnet hat. Seitdem hoffen einige, dass der neue Premierminister die dringend benötigte politische Reform bringen würde, während andere ihn als einen Insider der regierenden Partei betrachten, die die Macht seit 27 Jahren kontrolliert und aufgrund dessen keine Reform erwarten.

Die meisten Oppositionsparteiführer merkten an, dass die jüngste neue politische Haltung, die von Premierminister Abiy Ahmed und seinem Team angeführt wurde, die von der Position der Hardliner innerhalb der Regierungspartei abgelöst schien, eine willkommene Entwicklung war. Aber es gibt immer noch kein klares Zeichen, ob diese Gruppe von Menschen einen wirklich demokratischen und tiefgreifenden politischen Wandel herbeiführen oder ob sie nur oberflächliche Reformen durchführen wollten, um das Leben des autoritären Regimes der EPRDF zu verlängern. Die Leute argumentieren, dass sogar in einer Situation, in der der Premierminister für echte politische Veränderungen entschlossen sei, die TPLF, die das Militär und den Geheimdienst sowie den “wandernden Bandit-Kapitalismus” kontrolliert, eine ernsthafte Herausforderung und ein Stolperstein gegen die erwünschte Veränderung wäre.

Es ist ermutigend, dass die Gruppe um Lemma Megersa, Präsident der Oromo-Region, und der Premierminister selbst öffentlich “Ethiopianism” artikuliert haben, anstatt die ethnische Identität zu betonen; und dass sie Zeichen gezeigt hatten, dass sie die Rechte der einzelnen Bürger für von größter Wichtigkeit hielten. Allerdings hat der Premierminister bisher keine greifbaren politischen Maßnahmen ergriffen. Das Regime hält immer noch tausende politische Personen gefangen, das neue Kabinett schien kein Kabinett zu sein, das für den Wandel zusammengestellt wurde und der Ausnahmezustand ist immer noch vorhanden. Darüber hinaus folgte auf den Aufruf des Premierministers, die Opposition zu beteiligen, keine Einzelheiten darüber, wie und unter welchen Bedingungen das Regime mit der Opposition verhandeln möchte.

Ich bin der festen Überzeugung, dass es natürlich und gesund ist, dem neuen Premierminister, Abiy Ahmed, die Zeit zu geben, seine bei seiner Antrittsrede gemachten Zusagen umzusetzen, in denen er versprochen hat, das Land zusammenzubringen und einen Dialog mit allen Gruppen zu führen. Wie der griechische Fabelschreiber “Aesop” jedoch sagte, zählen wir unsere Hühner nicht, bevor sie geschlüpft sind, sondern wir müssen warten, bis eine gute Sache, die erwartet wird, wirklich passiert ist, bevor wir etwas über die aktuelle äthiopische Situation sagen.

Sineshaw Fekadesilassie

WhatsApp Image 2018-06-28 at 15.40.25

Sineshaw Fekadesilassie

 

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ መደበኛ ስብሰባ በ 05.05.18 በኑረንበርግ ከተማ ተካሄደ

News Report by Alemayehu kidanewold

Photo by Michael Mekonnen

በየሶስት ወሩ የሚያደርገው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ መደበኛ ስብሰባውን በ 05/05/2018 በኑረንበርግ ከተማ አካሄድዋል::

 

ስብሰባው ከ ቀኑ 2pm ሰአት ብዛት ያላቸው የድርጅቱ አባላት ወቅታዊ ስለሆነው የሃገራችን ሁኔታ በሰፊው ተወያይተዋል::

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ መደበኛ ስብሰባው የሃገራችን ኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ በዴያስፖራው ልፋት በስደት የሚገኙ ኢትዮጵያን ለፍትህ ፣ ለዴሞክራሲና ለአንድነት በተለያዩ ታላላቅ መድረኮች፣ ሰላማዊ ሰልፎች ፣ ተቃውሞዎች ድምጹን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ለብዙ አመታት ያሰማ ሲሆን ይህም ድካም ጥሩ ተስፋዎችን ይዞ መምጣቱን አመላክቶዋል::

 

በተለያዩ የሃገሪትዋ እስር ቤቶች የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች ፣ ጋዜጠኞች እና አክቲቪስቶች ከእስር ተፈተዋል::

አሁንም ቢሆን የኢትዮጵያ ህዝብ የቀሩትን ብዛት ያላቸውን የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ ያለ ምንም ቅደመ ሁኔታ እንዲለቀቁ እንዲሁም የአስቸኩዋይ ጊዜ አዋጁን እንዲያነሳና ፍትህና ዴሞክራሲ እንዲያሰፍን የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ ጥረቱን እነደሚቀጥል አስታውቆዋል::

አዲሱ ጠቅላይ ምንስትር ዶ/ር ኣብይ ኣህመድ በህዝብ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የመጡ ባይሆንም ለሃገራችን ህዝቦች እያደረጉ ያለውን የማቀራረብ የማስማማት እና ሃገራችን ከገባችበት ዘርፈ ብዙ ችግሮች የሚታደጉዋት እንዲሆን የጀመሩት መልካም መንገድ ድርጅታችን ጊዜ ሊሰጣችው እና በሚደረገው የዴሞክራሲ ግንባታም እገዛ ማድረግ እንዳለበት ተወያይተዋል::

 

“እኛም አገር ያለን ዜግነታችንም ኢትዮጵያዊ መስሎን ነበር! ከእርሻ ማሳችን ባዶ እጃችን ቀረን፤ ያለካሳ ከቤት ንብረታችን ልንፈናቀል ነው”

 

አንድ ሰው በአንድ አገር ወይም ክልል ወይም አከባቢ ሲወለድ ወዶና ፈቅዶ በራሱ ምርጫ የሚያድረገው አይደለም። ነገር ግን ሲወለድ ያገኘው ሲያድግ የተለማመደውና የተቀበለው የራሱ አገር ይሆናል። ወላጆቹም ቢሆኑ ድሃ ሆኑ ሀብታም ያለምንም ማንገራገር የሚቀበለውና ራሱን አሳምኖ ለነገ ኑሮ ራሱን የምያዘጋጅበት እንጂ ይህ የኔ አገር አይደለም ምርጫዬም አይደለም አልቀበለውም ብል ከአምዕምሮ ወጭ ሆኖ እንደምናገር ሰው እንጂ ተቀባይነት የለውም። እኛ በጋሞ ጎፋ ዞን ስንካለል፥ የጎፋ ብሔረሰብ ሆነን ስንኖር እንዲሁም በየቀበሌያችንና አከባቢያችን ስንወለድ መርጠን የተቀበልነው ሳይሆን የፈጣሪ ምርጫና ፈቃድ እንደሆነ ሁሉም የምገነዘበው ይመስለናል።

አሁን በየዕለት ኑሮአችን ጥላ ያጠላብን፥ መኖርን ያስመረረን፥ ግራ ያጋባን፥ መሄጃ ያሳጣን፥ መፍትሔ የነፈገን፥ አገራችን ኢትዮጵያ የእኛ እንዳልሆነች የምያሳየን በአከባቢው የመንግስት መዋቅር፥ በዞን መንግስት መዋቅርና በክልል የመንግስት መዋቅር የተቀመጡና አንዳንድ ከእነርሱ የጥቅም ተጋሪ የሆኑ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ተወካዮች ናቸው።

አገራችን ኢትዮጵያ የእኛም ከሆነች፥ እኛም ኢትዮጵያዊ ከሆንን ቀጥሎ ለማን አቤት እንደምንል ግራ ብገባንም ጉዳዩ የሚመለከተውና ሀላፊነት ያለው አካል መብታችንን እንዲያስከብርልን፥ ለጥያቄያችን መልስ እንድሰጠን፥ በደላችንን እንዲያይልን እኛ በደቡብ ክልል፥ በጋሞ ጋፋ ዞን፥ የደምባ ጎፋ ወረዳ የጉራዴ ቀበሌ አርሶ አደሮች ፍትሐዊና ትክክለኛ አስተዳደራዊ ምላሽ እንድሰጠን እንጠይቃለን፤ የአቤቱታ ጩኸታችንን እናሰማለን።

ከኦቶሎ ሳውላ የመንገድ ሥራ ተቋራጭ (ፋል የሚባል) በመንገድ ሥራው ምክንያት በእርሻችን ላይ ጎርፍ ለቆብን ከእርሻ መሬታችን ነጻ ወጥተናል። ጎርፉ ደለል፥ አሸዋና ጠጠር ስለቆለለብን እርሻችንን ማረስ አንችልም፥ ከጥቅም ውጭ ሆነናል። በተደጋጋሚ ለወረዳው አስተዳደር ጥያቄ አቅርበናል ሰሚ አጣን፥ ለዞን አስተዳደር በደብዳቤና በአካል ቀርበን ጠይቀናል፤ እንዲሁም ለደቡብ ክልል ቅሬታ ሰሚ አካል በደብዳቤና በአካል ቀርበን አቤት ብለናል። ላለፉት አምስት አመታት መፍትሔ ፍለጋ የተለያዩ በሮችን አንኳኩተናል፥ በትራንስፖርትና በአልጋ ኪሳችንን አራቁተናል፥ ድካምና እንግልት ደርሶብናል፥ ከአመራር አካላት ስድብና ዘለፋ ተፈራርቆብናል። ለረጅም ዓመታት ስናርስበት፥ ስንገለገልበት፥ ስንገብርበት፥ ልጆቻችንን ስናስተምርበት፥ ቤተሰቦቻችንን ስንመግብበት ለአገር ልማትና ዕድገት የደርሻችን ስንወጣ የኖርንበት መሬት ያለ ተገቢ ካሳና ተለዋጭ መሬት ሳይሰጠን መንገድ ተቀይሶበታል የጎርፍ መቀልበሻ ተቀዶበታል፤ ከእርሻ ማሳችን ነፃ ወጥተን ከነቤተሰቦቻችን ሜዳ ላይ ወድቀናል። ሰሚ ካለን የአስተዳደር ያለ! የፍትህ ያለህ! የሰሚ ያለህ! የፍርድ ያለህ! እንላለን።
ይህ ሳያንስ ሌላ ጫና፥ ሌላ በደል፥ ሌላ ማፈናቀል፥ ሌላ የፍትህ መንፈግ እየተፈፀመብን ነው። ይኽውም የጉራዴ ቀበሌ ነዋሪዎች ሳይስማሙበት፥ ካለፊቃዳቸው ውጭ ከዚህ በፊት በደንባ ጎፋ ወረዳ ሥር ሲተዳደር የነብረን ቀበሌ ወደ ከተማ መዋቅር በራሳቸው ፈቃድ በማን አለብኝነት ማዛወራቸው ነው። ያለ ህዝብ መስማማት፥ ያለበቂ ውይይትና ምክክር ከእንግዲህ ወዲህ የጉራዴ ማህበረሰብ የምተዳደረው በሳውላ ከተማ አስተዳደር መዋቅር ሥር ነው በማለት ባለቤት እንደለሌው ንብረት ገበያ ላይ አውጥተው አንዱ መዋቅር ለሌላኛው ሽያጭ አካሂደውብናል። ትናንትና የፈፀሙብን በደል ሳያንስ ከጋሞ ጎፋ ዞን ጋር በመመሳጠር ለአትክልቶቻችንና በእርሻችን ላፈራነው እህል ተገቢ ካሳና ግምት ሳይከፍሉ መሬታችንን ለመቀማት ፈልገው የሚያድረጉት ሤራ ስለሆነ የሚመለከተው አካል ቶሎ እንዲደርስልን እንጠይቃለን። ህይ ድርጊታቸው የሰው ሕይወት መጥፋትን፥ የንብረት ውድመትን፥ በአከባቢው የሰላም ውድመትን ሳይስከትል ተገቢ ምልሽ እንድሰጠን እናመለክታለን።
አንዳንድ የአስተዳደር አካላትና ጥቅም ፈላጊዎች ውስጥ ለውስጥ በህዝብ መካከል አለመተማመንን እየዘሩ በመንግስት ላይ ጥርጣረ እንዲፈጠር የሚያደርጉ አካላት ከሥልጣናቸው እንዲወርዱ እንዲሁም መልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱልን እንጠይቃለን። መብታችንን በጠየቅን ቁጥር ፀረ ሰላም ሀይሎች መባላችን ይቁም፥ ተገቢ ምልሽ ይሰጠን።
አርሶ አደሮች

US House Resolution on Ethiopia Passes

by Felix Horne
Human Rights Senior Researcher, Horn of Africa

Anti-government protest in Woliso, Ethiopia.

Today, the US House of Representatives passed a resolution encouraging Ethiopia’s government to increase respect for human rights, rule of law, and democracy. This non-binding resolution, combined with recent statements from the US Embassy in Addis, sends a strong signal to Ethiopia’s new prime minister that the US expects significant reforms ahead.

Resolution 128 was passed in large part because of Ethiopian-American voters concerned with the Ethiopian government’s rights record, who worked together to make themselves an important constituency. Their persistent efforts despite the efforts of the Ethiopian embassy and their Washington lobbyists led to an impressive 108 Congressional representatives from 32 states co-sponsoring this resolution. Hopefully they can build on this success and advocate for binding legislation on Ethiopia.

Amongst other things, the resolution calls for Ethiopia’s government “to allow an independent examination of the state of human rights in Ethiopia by a rapporteur appointed by the United Nations.” Ethiopia has repeatedly rebuffed efforts to investigate allegations of serious crimes by government forces and has not let in any UN Special Rapporteur to investigate allegations of abuse since 2007. With a new prime minister, now is the time for Ethiopia to change course and allow independent experts to investigate, including the Special Rapporteurs on torture and freedom of assembly.

Over the past two years, Ethiopia’s government security forces have arrested tens of thousands of people protesting government policies and have killed over 1,000 demonstrators. Torture in detention is rife, and independent media, civil society, and opposition parties are severely limited.

The United States, like many of Ethiopia’s international partners, is focused on collaborating with the country on counterterrorism efforts, peacekeeping, and economic growth. Yet for the partnerships to be effective, Ethiopia needs to be stable. And in light of the past two years’ sweeping protests, the question of stability is inextricably linked to Ethiopia’s harsh response to dissent and political opposition.

This resolution not only encourages the government to implement key reforms, but says that future US cooperation should be tied to Ethiopia’s “demonstrated commitment to democracy, the rule of law, and human rights.” Encouraging those reforms with measurable, specific, and transparent benchmarks in exchange for future cooperation is critical. It is also important that other countries follow the US Congress’ lead on tying support to tangible progress.

እነ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እንዲፈቱ ዓለም ዓቀፍ የመብት ተከራካሪዎች አሳሰቡ

 

ባለፈው እሁድ በድጋሚ ለእስር የተዳረጉት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ሌሎች ሰዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጥያቄ ቀረበ፡፡ ጥያቄው ከሀገር ውስጥ አልፎ በውጭው ዓለም የሚገኙ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች ጭምር ሲሆን፤ ስለ ጋዜጠኞች መብት የሚሟገቱ ድርጅቶችም የታሰሩት ሰዎች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ መግለጫ በማውጣት ላይ ይገኛሉ፡፡ ባለፈው እሁድ መጋቢት 16 ቀን 2010 በተመስገን ደሳለኝ መኖሪያ ቤት በተሰናዳ የምስጋና ፕሮግራም ላይ ታድመው የነበሩ 12 ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ ሰዎች በድጋሚ ለእስር መዳረጋቸው ይታወሳል፡፡

eskinder free

ዓለም ዓቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ሲፒጄ የእነ እስክንድር ነጋን መታሰር አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፣ ለእስር የተዳረጉት ሁሉም ሰዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ መንግስትን አሳስቧል፡፡ በዩናይትድ ስቴትስ የፍሎሪዳ ግዛት ሴናተር የሆኑት ማርኮ ሩቢኦ በውሸት በተመሰረተበት ክስ ለእስር ተዳርጎ ከሰባት ዓመት በኋላ በቅርቡ የተፈታው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና አብረውት የታሰሩት የፖለቲካ እስረኞች መፈታት አለባቸው ሲሉ አገዛዙን አሳስበዋል፡፡ ሌላው ዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም የሆነው አምነስቲ ኢንተርናሽናል በበኩሉ፤ የጋዜጠኞቹ እና ፖለቲከኞቹ መታሰር አሳፋሪ መሆኑን ገልጾ፣ በአስቸኳይ እንዲፈቱም ያሰራቸውን አገዛዝ አሳስቧል፡፡

የመብት ተቆርቋሪ ድርጅቶች በተናጠል ካወጡት የእስረኞች ይፈቱ መግለጫ በተጨማሪ፤ አርባ ዓለም ዓቀፍ እና በኢትዮጵያውያን የተቋቋሙ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ጋዜጠኞቹ እና ፖለቲከኞቹ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ቅንጅት ፈጥረው እየተንቀሳቀሱ ሲሆን፤ ሲፒጄም ይህን ስብስብ መቀላቀሉ ታውቋል፡፡ አርባዎቹ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች፣ ሰኞ ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ለሚሰየሙት ዶ/ር አብይ አህመድ በጻፉት ደብዳቤ፤ ጋዜጠኞቹ እና ፖለቲከኞቹ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ አሳስበዋል፡፡ ሁሉም የታሰሩት ያለ ምንም ክስ መሆኑን የጠቀሱት አርባዎቹ የመብት ተከራካሪ ድርጅቶች፤ እነ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የታሰሩትም አርብ የካቲት 23 ቀን 2010 በጸደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አማካይነት መሆኑንም በጋራ በጻፉት ደብዳቤ ገልጸዋል፡፡

የህሊና እስረኞቹ በአሁን ሰዓት ታስረው የሚገኙት በላፍቶ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኝ ፖሊስ ጣብያ ሲሆን፤ የእስር ቤት አያያዛቸውም ለበሽታ እና ለመሰል ጉዳቶች የሚያጋልጥ እንደሆነ ታውቋል፡፡ 5 በስምንት በሆኑ ሶስት ክፍሎች ውስጥ ከ200 ሰዎች ጋር የታሰሩት እነ እስክንድር ነጋ፤ ክፍሏ በጣም ጠባብ በመሆኗ ለመተኛትም ሆነ ለመቀመጥ እንዳልቻሉም ተነግሯል፡፡ በዚህ አስቸጋሪ የእስር ሁኔታ ላይ ከሚገኙት ታሳሪዎች አንዱ የሆነው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ከዚህ ቀደም በዝዋይ እስር ቤት ሳለ ያጋጠመው የወገብ ህመም አገርሽቶበት በትላንትናው ዕለት ሆስፒታል መግባቱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የእስር ቤቱ ወለል ወይም መሬት ቀዝቃዛ ሲሚንቶ መሆኑ፣ የታሳሪዎቹን የጤና ሁኔታ ለእንከን እንደሚያጋልጠው ተነግሯል፡፡

Image may contain: text

የዶክተር አቢይ መመረጥ፣ መጻኢ እድላቸውና ፈተናዎቻቸው

abiy

የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ)

“ምርጫችን መለያየት ወይም መበታተን ሳይሆን መደመር/አንድ መሆን ብቻ ነው። አማራና ኦሮሞ በወንፊት እንኳ እንደማይለያዩ ሠርገኛ ጤፍ ማለት ናቸው። ታሪካችን የአንድነትና በአንድነት አብሮ የመሥራት ታሪክ ነው፤ ለዚህም የፋሲል ግምብ ግምባታና አድዋ በቂ ምሣሌዎቻችን ናቸው። ይህ አገር የወረስነው ሳይሆን ከልጆቻችን የተዋስነው አገር ነው።” አቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ዶክተር አቢይ አህመድ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፤ ከላይ የተጠቀሰውን መሰል፤ በርካታ ቀስቃሽና አገር ወዳድ ንግግሮችን በማሰማታቸው በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ላይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገዝፈውና ተወዳጅ ሆነው ብቅ ያሉ ኢትዮጵያዊ ናቸው። በአገር አቀፍ ደረጃ ስማቸው አሁን ጎልቶ ተሰማ እንጂ፤ እነ አቶ ለማ መገርሳና አዲሱ ኦህዴድ ለጀመሩት ለውጥ እንደ አንድ ዋነኛ አጋር ሆነው፤ ድምጻቸውን አጥፍተው ሲሰሩ እንደቆዩ ይነገራል።

ሸንጎ በአንድ በኩል እንዲህ ዓይነት ችሎታና አገር ወዳድነት በአያሌው የተለገሳቸው ግለሰብ ለአገር መሪነት መመረጣቸው ደስ  የሚል ዜና መሆኑን እየገለጽን፤ በሌላ በኩል አገሪቱ አሁን ካለችበት የፖለቲካ ቀውስ አንጻር፤ በርካታ ጠጣርና ጠመዝማዛ ፈተናውች እንደሚገጥሟቸው ከወዲሁ ማሰብ እንችላለን። ከነዚህ ውስጥ ዋነኛው የመከላከያና የጸጥታ ሀይሎች በህወሃት እዝ ስር መሆናችው ነው። ይሁን እንጂ ዶክተር አቢይ ከመመረጣቸው በፊት ያሳዩትን ቁርጠኝነት ተከትለው ወደፊት ከተራመዱ (ለምሳሌ እኔ የማንም ቱቦ አልሆንም ያሉትን እናስታውሳልን) ህዝቡ ሲጠይቅና ሲዋደቅለት የቆየውን ለውጥ ለመተግበር አንዲት ቀጭን እድል ይኖራቸዋል ብለን እንገምታለን።

ይህም ቀጭን እድል ዶክተር አቢይ የሚያቋቁሙት መንግስት (ካቢኔ) ከህዝብ ጋር በተለይም ከወጣቱ ጋር የሚፈጥረው አጋርንት ነው። እስካሁን ከሰማነው ዶክተሩ በአማራና በኦሮሞ እንዲሁም በከፊል ደቡብ ህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት አላቸው። በቅልጥፍና ወጣቶች ተደራጅተውና ተቀናጅተው በመንቀሳቀስ የለውጡ አስተማማኝ ሃይል እንዲሆኑ መርዳት ይጠበቅባቸዋል ። ህጋዊ መድረኮችን በመጠቀም መንግስታቸው ክሌሎች ህዝቦች ጋር (ቤንሻንጉል፤ ጋምቤላ፤ ሱማሌ) የሚኖረውን ዝምድና ማጥበቅ;። አሁን በኢህአደግ ውስጥ ያለውን ወደ እርሳቸው ያጋደለውን የሃይል ሚዛን በመጠቀምና በኦሮሚያ ውስጥ ያላችውን የህዝብ ድጋፍና የለውጥ ፈለግ መሰረት በማድርግ ደፈር ያሉ የለውጥ እርምጃዎችን መውሰድ ይችላሉ። ከዚህም በተጨማሪ በፓርላማ ውስጥ ለውጥ ፈላጊ ግዛቶች ያላቸውን የቁጥር ብልጫ በአግባቡ በመጠቀም ህዝቡ የሚጠይቃቸውን ለውጦች ሊጀምሩና ወደ ቀጣዩ የለውጥ አቅጣጫ አገሪቱን ማድረስ ይችላሉ። ይህ እንግዲህ ቀጭኑ ግን ትልቁ እድላቸው ነው።፡

ጎታችና አፋኝ ሃይሎች የለውጡን ጉዞ ለማደናቀፍ በየደረጃው መሰናክል እንደሚፈጥሩ ሊታሰብ ይገባል። ከዚህ ውስጥ በዋናነት ሊጠቅስ የሚገባው ሰሞኑን የተጀመረው የለውጥ አራማጆችን እየለቀሙ ወደ እስር ቤት ማጎር ነው። ዓለምን ጉድ ባሰኘ የአፈና አካሄድ ከእስር ቤት ከወጡ ገና ጥቂት ቀናት ያስቆጠሩ ጋዜጠኞችንና የፖለቲካ መሪዎችን እንደገና መልሰው  ለእስር ሰቆቃ ዳርገዋቸዋል። ሸንጎ በሰላማዊ ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን እስራትና አፈና አጥብቆ ይኮንናል። የዶክቶር አቢይ ሃቀኛ የለውጥ ፈላጊነት የሚረጋገጠው ይህን በሰላማዊ ህዝብ ላይ የተቃጣ የመከራና የእስራት ጉዞ ማስቆም ሲችሉ ነው።  ህዝቡ እስካሁን የህወሃትን ደባ ተቋቁሞ ከመበተን አንድነትን፤ ከጥላቻ ፍቅርን፤ ከመራራቅ መቅረብን መርጧል። የዶክተር አቢይ መንግስት ስኬት ሊያመጣ የሚችልውና ከአደናቃፊዎቹም የሚመጣብትን ጥቃት ሊመክት የሚችለው  በህዝቡ ላይ እምነት ሲኖረውና ከህዝቡ ጋር ሲወዳጅ ብቻ ነው።

ዶ/ር አቢይ አሕመድ ይህንን አገር የመምራት ከፍተኛ ግዴታና ኃላፊነት ሲቀበሉ ከፊታቸው የተደቀኑ ብዙ ችግሮችና አማራጮች እንደሚጠብቋቸው ቢያውቁም፤ እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ፤ አማራጮቹን ለማየትና ብሎም ችግሮቹን ለማስወገድ ኃላፊነቱን እንደተረከቡ ሊያደርጓቸው በሚችሏቸው ጉዳዮች ዙሪያ ሸንጎ ሊያነሳቸው የሚሻቸው ዐበይት የፖለቲካ ኃሳቦች የሚከተለት ናቸው-

1.1         የአዲሱ ጠ/ሚኒስትር ዋነኛና ቀዳሚ ዓላማ መሆን የሚገባው፤ አንዳንድ መሠረታዊ ያልሆኑ ለውጦችን አድርጎ ኢሕአዴግን ከነጉድፉ ሥልጣን ላይ ማሰንበት ሳይሆን፤ ለሰላማዊ የሽግግር ሥርዓት በሩን መክፈት ይሆናል። ለሽግግር ሥርዓቱ በር ከፋች የሚሆኑ ርምጃዎች የሚከተሉትን ሊያጠቃልሉ ይገባል፦

  • ሳይውል ሳያድር በአጭር ጊዜ ውስጥ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማስወገድ
  • ለወደፊትም የመከላከያ ሰራዊት በሲቪል አስተዳደ ውስጥ ጣልቃ እንዳይገባ በህግ መገደብ
  • ድርጅታዊ የስለላና የግድያ መዋቅሮችን ማስወገድ፤
  • ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ባስቸኳይና ያላንዳች ቅድመ-ሁኔታ መፍታት፤

1.2        ሰላማዊ የሽግግር ሥርዓት በሮችን መክፈትና የቀዳሚም ሆነ የተባባሪነት ሚና ወስዶ የሰላም ኮንፈረንስ በአገር ውስጥ እንዲካሄድ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ወይም ከተቃዋሚ ድርጅቶች ጥሪ ጋር መተባበር፤

1.3        ተቃዋሚ ድርጅቶች ያላንዳች ተጽዕኖ በአገር ውስጥ እንዲንቀሳቀሱና የየራሳቸውን ድርጅት ምልመላ እያደረጉ ለምርጫ እንዲዘጋጁ ማበረታታትና ሕጋዊ ድጋፍም እንዲያገኙ ማድረግ፤

1.4        የሕዝቡን የመናገር፣ የመጻፍ የመሰብሰብና የመደራጀት መብቶችን ከአሁን ጀምሮ ማስከበር።

1.5     የፍትህ ስርዓቱን ለማስተካከል አሁን ያሉትን ዳኞች በሙሉ በማባረር፤ አዲስ የዳኞች መደባ ስርዓት ማቋቋም። 

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዶ/ር አቢይ አሕመድና በዙሪያቸው የሚያስቀምጧቸው ባለ-ራዕዮችና ዴሞክራሲያዊ አገር ወዳዶች እነዚህን ማድረግ ከቻሉ በርካታ የአገሪቱ ችግሮች ባመዛኙ ይቀረፋሉ የሚል ጽኑ ዕምነት አለን። እስካሁን በሕዝብ ላይ በአንዳንድ ወገኖች የተፈጸሙ ግፎችና ወንጀሎች ቀናቸውን ጠብቀው ፍትህ እንዲያገኙም በሩን ለውይይት መክፈት አግባብ ነው እንላለን።

ያለፍትህ ወደፊት መግፋት አይቻልምና ትውልዱ የሚጠይቀውን የፍትህ ጥያቄ በደፈናው ካሳለፍነው “አለባብሰው ቢያርሱ፤ በአረም ይመለሱ” እንዳይሆንብን ሸንጎ ጥብቅ ዕምነቱ ነው። ዶ/ር አቢይ ባሕር ዳር ላይ በተደረገው ስብሰባ ተገኝተው ተናገሩት የተባለውን ታሪካዊ ጥቅስ ሠፋ አድርገንና ለኢትዮጵያዊነትና ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን እንዲሠራ በማድረግ፤ “ኢትዮጵያዊነት በወንፊት እንኳ ተለይቶ የማይወጣ ሠርገኛ ጤፍ ማለት ነው” ብለን በማጠቃለል ነው።

አንድነት ኃይል ነው!

ሰላምና ፍትኅ ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Ethiopia: The Bounds of Non-Violent Struggle

by Addissu Admas

Ethiopia's state of emergency violates human rights

By temperament and conviction, I have always sought first peaceful resolutions to conflicts. I believe that human beings should exhaust all peaceful means at their disposal before embarking on any form of violent action, even against those who would not hesitate to rain violence and destruction upon them. I am certain that non-violent struggle is not only a moral choice, but a pragmatic one as well: it is far more effective at reaching desired goals with far less loss to human lives and possessions.

I still hold Mohandas Gandhi and Martin Luther King as exemplars of non-violent struggle. And everyone engaged in political struggle should always consult them first before considering any other form of struggle. But the question that nags everyone who is willing and determined to adopt their philosophy of non-violence is to what extent should one adhere to non-violent principles and mode of action. Is there, or indeed should there be, a boundary to one’s commitment to non-violent struggle? If yes, then, at what point?

Both Gandhi and King were profoundly moral persons who were determined, whatever the cost to their own lives, to bring about change to the status quo. They were impervious to being lured into violence. And they were deeply convinced that their powerful adversaries would eventually come to their senses, acknowledge their wrongdoing, and eventually reform. Their spirits were imbued with the optimistic view that human nature was essentially good, or at least capable of being led to do the right thing in the end. But most importantly, they conducted their struggles under political systems which adhered in principle, if not in action, to the rule of law and to human and citizenship rights.

However, like Orwell, I find it hard to imagine a Gandhi or a King emerging in Nazi Germany, the Soviet Union, or for that matter, in any totalitarian system of any shade or creed, live or defunct. Even though one can legitimately presume that there may have been men and women who, in their inscrutable ways, have tried to struggle against these inherently violent suppressive systems, we have no evidence of their achieving any transformative change on their landscape. Theorists and practitioners of non-violent struggle assure us that if we are ready to pursue non-violent struggle even in the most repressive regimes we will ultimately achieve our goals. Their belief is that no adversary will go as far as exterminating the people it oppresses. According to them, there would come at a certain time a point at which the adversary will become aware of the futility of its violence and adopt conciliatory ways to bring about change. I find again this to derive from an unbound optimistic perspective on human nature. How may one explain the Holocaust, the Stalinist and Maoist purges, Pol Pot’s killing fields, just to mention the most notorious examples of recent history? What these examples have shown is that human beings are indeed capable of committing genocide to maintain unchallenged power, or in the worse of cases, simply to show their power.

I say that non-violent struggle can emerge and grow mostly in States that are at least minimally adhering to democratic rules of governance. As long as there is a real commitment to democratic rights enshrined in the constitution, or as long as human and civil rights remain inviolate, it is not only expedient, but a moral imperative to conduct a non-violent political struggle to bring forth necessary changes. But when a democratic rule of law is suspended or simply suppressed; when the power in existence is determined to muzzle, persecute, torture, and kill with impunity, I see no justifiable reason to continue a non-violent struggle. I am not sure how allowing the adversary or opponent to trample my human and civil rights, to torture and kill me without any resistance on my part would do me any good or anyone else: what I have done is to simply submit to the cruelty and gratuitous violence of my oppressor in the deluded hope of transforming him or her into a moral being. I do not see any commendable value in this. Because, I am more convinced than ever that human beings would rather perpetrate unspeakable violence on their fellow human beings to maintain power than hear the voice of their conscience; presuming they have one.

I stand in awe of our youth, who, despite the determined effort of the TPLF’s regime to silence and suppress their voices with all the tools of violence at its disposal, have continued to struggle non-violently to bring about change. They have been merely exercising their human and civil rights enshrined in the Ethiopian constitution. And yet, the very same regime that continues to gloat for creating it, continues to trample it with utter disregard. Where in lies its credibility? Or for that matter its legitimacy? For all practical purposes, a regime which has violated time and again not only our constitutional rights, but even more tellingly our human rights, should be perceived as being no different from a gang of bandits. As indeed, the great Christian thinker St. Augustine said:

“Remove justice, and what are kingdoms but gangs of criminals on a large scale? What are criminal gangs but petty kingdoms? A gang is a group of men under the command of a leader, bound by a compact of association, in which plunder is divided according to an agreed convention”

If this villainy wins so many recruits from the ranks of the demoralized that it acquires territory, establishes a base, captures cities and subdues people, it then openly arrogates to itself the title of kingdom, which is conferred on it in the eyes of the world, not by the renouncing of aggression but the attainment of impunity” [City of God, Book IV.4]

This, in effect, is what we have in reality in Ethiopia today. Where in lies the legitimacy of the TPLF once it has turned its back on the very basic human and civil rights, and opted violence over the rule of law? How can it consider itself “a government” when all it does is plunder and rob the country blind? The TPLF has in fact shown that it will do anything, even plunge the country into civil war rather than relinquish power. Should the determination of our youth to bring change rely entirely on non-violent struggle? Can we ask them to be tortured and slaughtered by a regime determined to quash all opposition by any means necessary? Can we ask them to be martyrs of an enemy that has no pangs of conscience? The question is not one of moral fortitude only, but one of viability as well!

No one should be naïve as to believe that this regime will change course now or ever. If we understand by change a fair and transparent democratic election, we might as well simply ask directly the TPLF to step down from its high perch. This is what it amounts to in truth! The question then is what alternative is left for Ethiopians in the face of this regime’s determination to use all instruments of repression and violence to silence and subdue all opposition voices?

It is not only natural, but also a moral duty to stand up to a power that has clearly demonstrated to have no qualms in using all instruments of violence to rob us not only of our human and civil rights, but also of our very own lives: I see no merit in sacrificing one’s life if that life, which is so precious to myself and to so many of my fellow human beings, amounts to nothing to my opponent. Indeed, my core moral duty should be not only to make it count, but to defend it by any means necessary.

The second article of the Amendment of the Constitution of the United States declares that “the people should have the right to keep and bear arms”. This right may appear obsolete and unnecessary in highly organized and democratized nations of today. But one should not lose sight of its fundamental import. It is perhaps more meant to preempt the emergence of tyrannical forms of government than the mere defense of one’s property and life! Ethiopians have been deprived systematically of their ability to defend themselves since the advent of the Derg. Until then, it was neither illegal nor uncustomary to bear arm for one’s defense. By the very act of dispossessing people of their arms, not only was the Derg able to effectively quash all opposition, but it also paved the way for the current regime to continue to do the same.

Even though I continue to believe in the moral and practical superiority of the non-violent struggle, I cannot with good conscience defend its practice under all circumstances and under all political regimes. One must in essence make a realistic cost benefit analysis if a non-violent struggle should be pursued or abandoned. If after a careful and thorough deliberation it is deemed that continuing it will only result in loss of lives without any tangible result, it is incumbent on the people to adopt a strategy to achieve their goals by other means. I believe the most reasonable alternative to non-violent struggle is to organize communities of people for self-defense.

The TPLF and the regime it has created is now at the point of desperation and it will resort to every known or unknown extreme measures to preserve its power. Like a cornered animal it is capable of the most violent reaction. We have had already a taste for this since the outset of the first State of Emergency. It is in fact absolutely high time for the Ethiopian people to rise and prepare not to wage war, but arm to defend themselves against a regime which has clearly shown its willingness to clobber, torture, maim, imprison and kill out of the mess it alone has created. Not to prepare for what promises to be the final showdown with this cruel, divisive and predatory regime is utter irresponsibility!

I therefore urge especially the young to be ready not only to defend their rights but also their lives, because it is by now clear that they have an enemy willing to destroy them and their nation rather than surrender to the will of the people.

የለማ ኦህዴድ ፈተና

 

ጦርነት ታውጆበታል። አስቸኳይ ጊዜ ተደንግጎበታል። ባለስልጣናቱ መናገር አይችሉም። ከተናገሩ ይታሰራሉ። የታሰሩትን የሚከታተላቸው የለም። ዋናዎቹም በትግራይ ደህንነቶችና በሳሞራ ቅልብ ወታደሮች ዓይን ስር ናቸው። መፈናፈኛ ለጊዜው የለም። ድምጻቸው ጠፍቷል። የትግራይ ገዢ ቡድን ባለስልጣናት በየመድረኩ ሲያስካኩ ሲፎክሩ፡ የለማ ኦህዴድ ሰዎች ግን ትንፋሻቸው እንኳን የለም። ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ዞን ድረስ ያለው የለማ ኦህዴድ መዋቅር በትግራይ ደህንነቶች እየተበረበረ አመራሮቹ በኮማንድ ፖስቱ ሰራዊት እየታደኑ ወደ ግዞት እስር ቤቶች እየተወረወሩ ናቸው። የአቶ ለማን የተስፋ መልዕክቶችና ቆራጥ ንግግሮች መከታ ጋሻ አድርገው ለለውጥ የተነሱ ባለሀብቶችም በአባዱላና በአቶ ድንቁ ጠቋሚነት እየተለቀሙ ወደ ማዕከላዊ በመወሰድ ላይ ናቸው።

የትግራዩ ገዡ ቡድን ጥድፊያ ላይ ነው። ጊዜ መስጠት አልፈለገም። እነለማንና አብይን በስብሰባና ግምገማ አፍኖ መዋቅራቸውን በማወላለቁ ዘመቻ ላይ ተጠምዷል። በመካሄድ ላይ ያለውን የኢህአዴግ የስራ አስፈጻሚ ስብሰባ በተመለከተ ከባልደረቦቼ ኤርሚያስ ለገሰና ምናላቸው ስማቸው ጋር በኢሳት እፍታ ፕሮግራም ላይ ውይይት ባደረኩበት ጊዜ የተገለጠልኝ እነ ለማ መታገታቸውን ነው። መግለጫ መስጠት አይችሉም። ክልላቸውን እያስተዳደሩ አይደለም። ካቢኔያቸውን መገናኘትም አይችሉም እየተባለ ነው። ከጨዋታ ውጪ ተደርገዋል። ኤርሚያ ለገሰ መፈንቅለ ድርጅት ተካሂዷል ይላል። ውይይቱን ብታዳምጡ አትከስሩም። በማዳመጥ ለምታጠፉበት ጊዜ የሚቆጫችሁ እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ማስፈንጠሪያውን ከዚህ ጽሁፍ ግርጌ አኖርላችኋለሁ።

እናም የእነለማ ኦህዴድ በጅቦች ተከቧል። ከህግ ውጭ፡ አሰራሩ በማይፈቅድ ሁኔታ የትግራዩን ገዢ ቡድን ከሞት ለማዳን በቀቢጸ ተስፋ የተሰለፉት የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ነባር አመራሮች ከያሉበት ተለቃቅመው ገብተዋል። የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አይደሉም። ምንም ውስጥ ምንም የላቸውም። ነገር ግን ጊዜው ቀውጢ ነው። የሞት ሽረት ትግል የሚካሄድበት ነው። 11ኛው ሰዓት ላይ የሚገኘውን የትግራይ ገዢ ቡድን ህልውና ለማትረፍ መረባረብ አለባቸው። የሚቧጠውን ቧጠው፡ የሚነከሰውንም ነክሰው ማፊያ ድርጅታቸውን ለማዳን ከስብሰባ አዳራሽ ገብተዋል። ይሉኝታን ከነመፈጠሩም የማያውቁት፡ ህሊናቸውን ገና ተከዜን ተሻግረው ሲዘልቁ በእንዶድ አጥበው የተገላገሉት፡ ከዕውቀትም፡ ከዕውነትም የተጣሉት፡ የዘመኑ ጎልያዶች፡ ተጠራርተው ተሰይመዋል። የመጨረሻ ሙከራ ነው። ይህ ስብሰባ ሁሉ ነገር ይለይለታል። ጀጋኑ፡ ተጋዳላይ፡ ወዲዎች!

እርጅናና የአልኮል ሱስ የተንኮልና ሴራ አቅሙን ያላዳከመው ስብሃት ነጋ ያጉረጠርጣል። የማይድን በሽታ የሚያሰቃየውና በመድሃኒት ጉልበት ቆሞ የሚሄደው ስዩም መስፍን ለዚህ ስብሰባ የሚሆን አቅም አላጣም። ቴድሮስ ሀጎስ ከመቀሌ ገብቷል። አለቃ ጸጋዬ በርሄ ከቴልሃቪቭ በሮ መጥቷል። የስብሃት ነጋ ምርኩዝ ጠባቂ የሚባለው አባዲ ዘሙም አልቀረም። የሙስናው ባላባት ወዲ አባይ ጸሃዬ ፊት ወንበር ላይ ጉብ ብሏል። እነዚህ ስድስት የትግራይ ገዢ ቡድን ነባር አመራሮች በህውሀትም ሆነ በኢህ አዴግ ስራ አስፈጻሚ ውስጥ የሉም። ግን ተሰይመዋል። በወሳኙ ስብሰባ ላይ ወንበር ይዘው ተቀምጠዋል። ኤርሚያስ እነዚህን ሰዎች በዱር እንስሳ መስሏቸዋል። የትግራይ የበላይነት ላይ አደጋ የደቀኑትን ሰልቅጠው ለመብላት የተሰለፉ አውሬዎች።

ስብሰባው ሀገ ወጥ ነው። የእነዚህ ሰዎች መገኘት ብቻውን ጨዋታውን ያፈርሰዋል። ሳይጀመር ውጤቱ የታወቀ ስብሰባ ላይ እነለማ ምን ይሰራሉ? ምን ይጠብቃሉ? የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም። በእርግጥ ጥያቄው ተገቢ ነው። እነዚህ የትግራይ ቡድን ነባር አመራሮች የተገኙት ለምን እንደሆነ ይታወቃል። ከየብሄራዊ ድርጅቶቹ ዘጠኝ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ብቻ በሚሳተፉበት ስብሰባ ላይ ያለስልጣናቸው፡ ያለወንበራቸው ወንበር ይዘው የተቀመጡት እነስብሃት ምን እያሸተቱ እንዳለ ከማንም የተሰወረ አይደለም። ለማጣፈጫነት ከሌላውም ድርጅት ነባር የሚባሉ አመራሮች መግባታቸው አልቀረም። እንደነካሱ ኢላላ ዓይነት ህወሀትን በጉርምስናው ዘመኑ የተጠመቀ የደኢህዴን አመራርም በስብሰባው ላይ ተገኝቷል። ዓላማው የእነስብሃትን መገኘት ምክንያታዊ ለማድረግ ነው። ደግሞም ካሱ ኢላላ ከስብሃት በላይ ህወሀት መሆኑን ለሚያውቁ የቅርብ ሰዎች ጉዳዩ በሚገባ ግልጽ ይሆንላቸዋል።

እንግዲህ እነስብሃት ተሰባስበው የገቡበት ስብሰባ በዝግ እየተካሄደ ነው። የትግራይ ገዢ ቡድንን ህልውና በማይናወጥ መሰረት ላይ ተክሎ ዳግም የኢትዮጵያን ህዝብ ረግጦና ጨፍልቆ ለመግዛት የሚያስችል አቋም ላይ ለመድረስ እንደሆነ አያያዙ ይመሰክራል። ከአዳራሹ ውስጥ እነስብሃት የለማን ቡድን ወጥረው ይዘዋል። ከአዳራሽ ውጪ ኮማንድ ፖስቱ የለማን መዋቅር እየመታ ነው። እነለማ ከውስጥም ከውጭም እየተጠቁ ናቸው። የትግራይ ገዢ ቡድን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የፈለገበት ምክንያት ከመቼውም ጊዜ በላይ ፍንትው ብሎ የታየበት ሆኗል። በረከት ስምዖንን ጨምሮ መላው የደኢህዴን አመራር እነለማ ላይ የጭቃ ጅራፍ እየሰነዘረ እንደሆነም ይሰማል። እነስብሃት ሂሳብ ሰርተው የገቡበትን ትወና በረከት፡ ካሱና ሌሎች በሚገባ እየተጫወቱት ነው።

የአጋች ታጋች ድራማው ቀጥሏል። እነለማ በአውሬዎች ተከበዋል። ጥያቄው በዚህ ሁኔታ እነለማ ምን ሊያደርጉ ይችላሉ? የሚል መሆን አለበት። ምን ምርጫ አላቸው? ከካቢኔው የተቆራረጠ፡ አፉ የተሸበበ፡ መተንፈስ ብቻ የተፈቀደለት የለማ አመራር በዚህ ወቅት ላይ ተስፋው ማን ነው? በእርግጥ ከስብሰባው አዳራሽ ምን እየተካሄደ እንዳለ ዝርዝር መረጃ ማግኘት አልተቻለም። ሽፈራው ሽጉጤ የሚባል ሰው ብቅ ጥልቅ እያለ ከሚወረውራት ቁራጭ መረጃ በቀር ሌላ ነገር የለም። ጭምጭምታዎች የሚያመላክቱት እነለማ በተከላካይነት መስመር ላይ መሆናቸውን ነው። አቅም እያጡ የመጡ ይመስላል። ጓዶቻቸውን ከጅቦች መንጋ ማስጣል ያልቻሉት እነለማ የታዬ ደንደአ፡ የአምስት ከፍተኛ የኦህዴድ አመራሮች እስር ላይ ዝምታቸው የሚነግረን ያሉበት ሁኔታ እጅግ ፈታኝ መሆኑን ነው።

በእርግጥ እነለማ በመጨረሻ ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ የሚያውቁት እነሱ ብቻ ናቸው። ሁለት ምርጫዎች ግን አላቸው። አንደኛው የአውሬዎቹን የሚያፏጭ ጥርስ አንበርክኳቸው፡ እጅ ሰጥተው ኦህዴድን ወደ ቀድሞው የአሽከርነት ዘመኑ በመመለስ በአሳፋሪ የታሪክ ገጽ ላይ ስማቸው ትተው ማለፍ ነው። ሁለተኛው ምርጫ የአወሬዎቹን ጥርስ ለማራገፍ ቆርጦ የተነሳውን ህዝባቸውን ተስፋ አድርገው መፈንቅለ ስብሰባ ከተካሄደበት አዳራሽ ውልቅ ብሎ መውጣት ነው። ሁለቱም ምርጫዎች ዋጋ ማስከፈላቸው አይቀርም። የመጀመሪያው ምርጫ ለእነለማ የቁም ሞት ነው። የእነስብሃትን የተሳለ ቢላዋ በመፍራት በተዘጋጀው ወጥመድ ውስጥ ዘው ብሎ መግባትን ምርጫቸው ካደረጉ የእነለማ ታሪክ በክህደት መዝገብ ላይ ሰፍሮ ሲወቀሱ ይኖራሉ። እየሰጠመ ካለው መርከብ ጋር አብረው ሰጥመው ከትውልድ ትውልድ እየተረገሙ ይነሳሉ።

ምርጫቸው ሁለተኛው ከሆነ ግን በኢትዮጵያ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ በመክፈት ሲወደሱ ይኖራሉ። ህዝባቸው ተነስቷል። የትግራዩን ገዢ ቡድን እያንቆራጠጠ ነው። በማያቋርጥ ህዝባዊ ማዕበል እያላጋው ነው። ይህ የህዝብ ሃይል እነዚህን የዘመኑ ጉግማንጉጎችን ጠራርጎ የታሪክ ቆሻሻ በምድረግ ሊቀብራቸው ከጫፍ ደርሷል። እነለማ ሁለተኛውን ምርጫ ከተከተሉ የሚከፍሉት ጊዜያዊ ዋጋ ነው። ምናልባትም እስር። ይሄው ጓዶቻቸው እየታሰሩም አይደል?! እነታዬ ደንደአ የታሰሩት ሰርቀው አይደለም። ነፍስ አጥፍተው አይደለም። ለቆሙለት መርህና የህዝብ ወገኝተኝነት እስከመጨረሻው ቃላቸውን በመጠበቃቸው ነው። ታዲያ እነለማ ምን ያስፈራቸዋል? እነታዬ እየከፈሉ ካሉት መስዋዕትነት በላይ ምን ዋጋ ሊከፍሉ እጅ ይሰጣሉ?

ይህ ሳምንት የለማ ኦህዴድ ቁርጡ ይለይለታል!!!!!

የኢትዮጵያው ፓርላማ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማጽደቁን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አወገዘ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 23/2010) የኢትዮጵያው ፓርላማ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማጽደቁን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አወገዘ። አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ተቋም አምነስቲ ኢንተርናሽናል እንዳለው ፓርላማው የሕዝቡን ድምጽ ከመስማት ይልቅ አፈናን ለማራመድ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማጽደቁ እጅግ የሚያበሳጭና ሃላፊነት የጎደለው ነው። የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ዋና ጸሐፊ ሳሊል ሸቲ የኢትዮጵያ ፓርላማ በዚህ አስቸጋሪና የፖለቲካ ቀውስ በተፈጠረበት ሁኔታ የሕዝቡን ድምጽ ሊሰማ ይገባ ነበር ብለዋል። አሁን የሚያስፈልገው የሕዝቡን ሰብአዊ መብት ማክበር እንጂ አፈና የሚያመጣው መፍትሄ የለምም ነው ያሉት። እንደ ዋና ጸሃፊው ሳሊል ሻቲ ገለጻ በኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት ተደንግገው በነበሩ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆች ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ረገጣዎች ተፈጽመዋል። እነዚህም ግድያዎች ጅምላ እስሮችና በሃይል መፈናቀልን እንደሚጨምርም ነው የገለጹት። እናም አሁን ሌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ማጽደቅ ተመሳሳይ ሕገወጥና በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት የሌላቸውን የሰብአዊ መብት ረገጣዎች እንዲፈጸሙ መስማማት ነው ባይ ናቸው። የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ዋና ጸሃፊዋ ፓርላማው የሕዝቡን ድምጽ ከመስማት ይልቅ አፈናን መምረጡ እጅግ የሚያበሳጭና ሃላፊነት የጎደለው ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የፓርላማ አባላት አዋጁን እንዳያጸድቁ በሕዝብም ሆነ በአምነስቲ ኢንተርናሽናል በኩል ቢጠየቁም በጉዳዩ ላይ 88ቱ አባላት ቢቃወሙም 346ቱ የድጋፍ ድምጽ ሰጥተዋል። ይህ ቁጥር ግን ከፓርላማው ጠቅላላ አባላት 2/3ኛ ድምጽ እንዳልሆነ ይታወቃል። ስለሆነም ፓርላማው ቁጥሩን አስተካክሎ የ395 ድምጽ ድጋፍ ተገኝቷል ማለቱ ሁኔታውን አወዛጋቢ አድርጎታል።

amnesty-international-logo-1

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ መደበኛ ስብሰባውን በአሻፍንበርግ ከተማ አካሄደ

News Report by Alemayehu kidanewold

Photo by Michael Mekonnen

በየሶስት ወሩ የሚያደርገው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ መደበኛ ስብሰባውን February 10,2018 በአሻፍንበርግ ከተማ አካሄድዋል:: በስብሰባው ላይም ብዛት ያላቸው የድርጅቱ አባላት የተገኙ ሲሆን ወቅታዊ ሰለሆነውም የሃገራችን ሁኔታ በሰፊው ተወያይተዋል::

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ መደበኛ ስብሰባውን በድርጅቱ ዋና ሊቀመንበር በአቶ ልዑል ቀስቅስ የመክፈቻ ንግግርና የሃገራችን የወቅቱን የፖተቲካ ሁኔት በማንሳት የተጀመረውን ትግልና የህዝብ እንቢተኝነትን በመደገፍ ምንጊዜም ከጎኑ ልንቆምለት እንደሚገባ በአጽንኦት ተናግረዋል::

የወያኔ ስርአት ሃያ ሰባት አመት ሙሉ ህዝብን ከህዝብ በማጋጨት የራሱን የስልጣን እድሜ ለማራዘም የሚያደርገውን ያለፈበትን ብልጠት በቃህ ልንለውና ማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ ብሄርን ከብሄር ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩትን ሰዎች ለይቶ በማወቅ እጅ ለእጅ ተያይዞ ለአንድ አላማ በጋራ መቆም እንደሚገባውም አሳስበዋል::

ተሳታፊዎቹም አሁን የደረስንበት የለውጥ ሰአት በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን ብዙዎች የተሰዉበትና ብዙዎችም ለእስር ፣ ለእንግልትና ለስደት ያበቃ በመሆኑ በምንም ተአምር ተመልሶ እንዳይገለበጥ እና ተመልሰን ወደ ድሮው ሰቃይና መከራ ላለመግባት ሁሉም ለውጥ ፣ ሰላምና ዲሞክራሲ ወዳድ ኢትዮጵያዊን በአንድነት ሊቆምና በጋራ መታገል እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል::

የኢትዮጵያ መንግስት ከሁሉም ወገኖች ጋር ሁሉን አቀፍ ንግግር እንዲጀምር የአውሮፓ ህብረት አሳሰበ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 12/2010) የኢትዮጵያ መንግስት ከሁሉም ወገኖች ጋር ሁሉን አቀፍ ንግግር እንዲጀምር የአውሮፓ ህብረት አሳሰበ። የጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በድንገት ከስልጣን የመልቀቅ ርምጃም በሃገሪቱ ያልተጠበቁ ሁኔታዎችን መደቀኑን ህብረቱ አስታወቋል። የአውሮፓ ህብረት ዛሬ ባሰራጨው በዚህ መግለጫ የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ እንደገና መታወጁም በዘላቂ መፍትሄ ጥረቱ ላይ አደጋ መደቀኑንም ገልጿል። በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር የሚዋቀረው መንግስት የተጀመሩ በጎ ርምጃዎችን አጠናክሮ እንዲቀጥል ሙሉ አቅም ሊኖረው እንደሚገባም አሳስቧል። ከሚመለከታቸው ወገኖች ጋር የሚደረግ ንግግር ለቀውሱ ዘላቂና ሰላማዊ መፍትሄ እንደሚያመጣ የገለጸው የአውሮፓ ህብረት ባለስልጣናት፣ተቃዋሚዎች፣መገናኛ ብዙሃንና ሲቪል ሶሳይቲ መካከል ንግግር እንዲጀመርም ጥሪ አቅርቧል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንደገና ተመልሶ መምጣቱ ዘላቂ መፍትሄ ፍለጋውን ለአደጋ ማጋለጡን ሆኖም በአጭር ጊዜ ገደብ ውስጥ መፍትሄ እንዲያገኝ ጥሪ ቀርቧል። በሃገሪቱ ሕገ መንግስት የሰፈሩ ሰብአዊ መብቶች እንዲሁም መሰረታዊ ነጻነቶች እንደተጠበቁና የአመጽ ድርጊቶችም እንዲወግዱ የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይና ሴኪዩሪቲ ፖሊሲ ቃል አቀባይዋ ካትሪን ሬይ በኩል ባወጣው መገለጫ አሳስቧል።

flag

የእነ በቀለ ገርባ ክስ ተቋረጠ

የእነ በቀለ ገርባ ክስ የተቋረጠው… በእነ ጃዋር የአመጽ ጥሪ ወይስ በመንግሥት ዕቅድ? እነ ኦቦ ለማ የእነ ኦቦ በቀለ ገርባን ክስ አስቋረጡ ወይስ የፌዴራል መንግሥት አመጹን ተከትሎ ወሰነው?
(የኦሮሞ ሕዝብ፣ የእነ ጃዋር እና የእነ ለማ ፖለቲካዊ አጨዋወት አንድ አቅጣጫን የያዘ ይመስላል። የሚፈልጉት ሁሉ እየሆነ ነውና።)

የሀገራሽን ጉምቱ ጉምቱ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች ከጠባቡ ወህኒ ቤት እየወጡ ነው። እንኳን በጠባቡ ከመታሰር በሰፊው ወደ መታፈን መጥታችሁ ተቀላቀላችሁን ብለናል።

ብአዴን ስብሰባ ላይ ነው። ብአዴን አማራን እወክላለሁ የሚል ፖለቲካዊ ንቅናቄ ነው። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጆች አባላት ያሉት ድርጅት ነው። (ቆይ ግን ከዚህ ላይ ብአዴንን ምን አስነሳኝ? 🙂 ) “ብአዴን ቢሰበሰብ ባይሰበሰብ… ቢመክር ባይመክር… ምን ይጠቅማል? ምንስ ለውጥ ያመጣል?” ብሎ ለማቃለል ይከብዳል። ማን ያውቃል… ብአዴንም ተለውጦ የምር የአማራ ሕዝብ ትምክህት ይሆን ይሆናል። ኦህዴድን በዚህ ደረጃ የኦሮም ሕዝብ ልብና ሳንባ ይሆናል ብሎ ማን ገምቶ ነበር??? እና ከብአዴንስ በጎውን ብንመኝ ማን ከልክሎን? አንዳንዴ… በፖለቲካ ዓለም ጠላቴ ያልኸው ነፃ አውጭ ወዳጅህ የመሆን ዕድሉ ዝግ አይደለም።

ለማንኛውም… የሀገሬ ፖለቲካ… ያው የአፍሪካ ፖለቲካ ነው። ከግጭትና ከደም ለመጽዳት ገና ብዙ ዘመናትንና ትውልድን ይጨርሳል።

27749995_1643343012425444_1284994562179587141_n