መኪና ከውጭ ሲያስገቡ እቃ እየጠፋባቸው የተቸገሩ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን የመኪና አስመጪዎች ቅሬታ እያሰሙ ይገኛሉ።
መኪናቸውን በኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክ አገልግሎት ድርጅት በኩል ከጅቡቲ ወደ ደረቅ ወደብ በሚያስገቡት ሰዓት እንደ ወንበር እና ጎማ የመሳሰሉ ነገሮች እየተሰረቁባቸው እና ለከፍተኛ ወጪ እንደተዳረጉ ይናገራሉ። የመኪና አስጫኞቹን ወቀሳ እና የድርጅቱን ምላሽ አግኝተናል።
ያነጋገርናቸው ከአውሮፓ መኪና ወደ ኢትዮጵያ የሚያስገቡ ነጋዴ እና ያስመጪ ንግድ ፍቃድ ስለሌላቸው፤ ፍቃድ ካለው ጓደኛቸው ጋር ተዋውለው መኪና ያስገቡ ግለሰብን ነው። ለግለሰቦቹ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክ አገልግሎት ድርጅት የኢንሹራንስ እና የካሳ ክፍል ዳሬክተር የሆኑት አቶ ያሬድ ሽፈራው ለወቀሳዎቹ የሰጡት ምላሽ አለ።
ሁሉንም ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።
ልደት አበበ
ነጋሽ መሀመድ
AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC