Archive | September 28, 2014

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ /EPPFG/ የጀርመንን መንግስትን ጨምሮ ለአለም ታላላቅ መንግስታትና ድርጅቶች ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ ባለ 6 ገጽ ደብዳቤውን አቀረበ

EPPFG Stamp 2

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ የጀርመንን መንግስትን ጨምሮ ለአለም ታላላቅ መንግስታትና ድርጅቶች ባለ 6 ገጽ ደብዳቤውን አቀረበ::

ድርጅቱ በደብዳቤው የወያኔን የ 23 አመት የግፍና የጭካኔ አገዛዝ አንድ በአንድ ጠቅሶ ያቀረበ ሲሆን ይህም መቀጠል እንደሌለበት ያመነው  የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ ጠንክሮ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ዘግቧል:: ሃገራችን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት በማዕድን ሃብትዋ እና በስው ሃይል ትልቅ ብትሆንም በአስተዳደር ችግር ግን በአለም ከመጨረሻዎቹ ሃገሮች ተርታ ተመድባ መቀመጥዋ ለዚህ ትግል እንዳነሳሳውም ገልጾዋል::

ደብዳቤውንም :-

  • ለጀርመን መንግስት
  • ለአውሮፓ ህብረት
  • ለ አሜሪካ እስቴት ዲፓርትመንት
  • ለአምነስቲ ኢንተርናሽናል
  • ለጀኖሳይድ ዎች መላኩን ኣሳውቆዋል

ሙሉውን ንባብ ይህን PDF በመጫን እንድታነቡት በአክብሮት እንጋብዛለን

ሕግ መንግሥታዊነት እና የሐሳብ ነጻነት በኢትዮጵያ /በዞን ዘጠኝ ጦማርያን/

/ሁሉም ሰው ሊያነበው የሚገባ/

ዞን ዘጠኝ የአራማጆች እና ጦማሪዎች ኢ-መደበኛ ቡድን ነው፡፡ ቡድኑ በአብዛኛው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ
በጦማሩ አስተያየቶችንና ትንታኔዎችን በማስፈር እና በየሦስት ወሩ የበይነመረብ ዘመቻ በማካሄድ
የአራማጅነት ሥራ ይሠራል፡፡ ከተመሠረተ ጀምሮ በአንድ ዓመት ውስጥ ሦስት ዘመቻዎችን (በሕገ
መንግሥቱ ይከበር፣ የሐሳብ ነጻነት ይከበር፣ እና የሰላማዊ ሰልፍ ይከበር በሚል) ያካሄደ ሲሆን ከ150
በላይ ጽሑፎችንም በጦማሩ በኩል አስተናግዷል፡፡
ከነዚህ ጦማሮች መካከል አብዛኛዎቹን በዚህ ጥራዝ ውስጥ ያዘጋጀናቸው ሲሆን፣ በወጡበት ቅደም
ተከተል ከማዘጋጀት ይልቅ በየርእሰ ጉዳዩ በማሰባሰብ አንባቢ በመረጠው ርዕስ ላይ አትኩሮ እንዲያነብ
በማድረግ አሰናድተነዋል፡፡ ይህንን በምናደርግበት ሰዓት የዞን ዘጠኝ አባላት የጻፉትን በሙሉ ስማቸውን
ሳንጠቅስ ያስተናገድን ቢሆንም፣ ከሌሎች ሰዎች ተልከውልን በጦማራችን ያስተናገድናቸውን ጽሑፎች
ጸሐፊዎች ግን ገልፀናል፡፡
ጽሑፎቹ በተለያዩ ጊዜ የተጻፉ እንደመሆናቸውና የተጻፉበት ጊዜንም የሚያንፀባርቁ በመሆናቸው ብሎም
ጦማሩ ላይ የሰፈሩበትን መልክ ሳንቀይር የሰበሰብናቸው በመሆኑ ያለፈባቸው ነገሮች ሊያጋጥሙ
ይችላሉ፤ በተጨማሪም ጥቃቅን የአርትኦት እንከኖች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ አንባቢዎች፣ እነዚህን ክፍተቶች
እየሞሉ እንዲያነቡ ከይቅርታጋ እንጠይቃለን፡፡
ጽሑፎቹን ሰብስበን በኤሌክትሮኒክ ኮፒ ማስቀመጥ ያስፈለገን፣ ለወደፊቱ ማነፃፀሪያ ይሆናሉ ብለን
በማመናችን መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
መልካም ንባብ!

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ ከታች ያለውን Pdf ይጫኑ

Zone9 – Compiled Book of Year One
Email: zone9ners@gmail.com
Twitter: @zone9ners